"In your light shall we see light" Psalm 36:9
መደበኛ(ቋሚ) ማስታወቂያ
ልዩ ማስታወቂያ
-
የአምልኮ ፕሮግራም ዘወትር እሁድ ከ 15-18፡00\ በመጨረሻም ህብረት የምናደርበት የሻይ ጊዜ በጋራ ይኖረናል።
-
ለታዳጊዎች ዘወትር እሑድ ከ15፡00-17፡00 ሰዓት እና ረቡዕ በየ15 ቀኑ ከ17፡00 ጀምሮ መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጣል።
-
የYoung adult ፕሮግራም ሐሙስ ምሽት ከ18፡00-20፡00
-
አርብ እለት ከምሽቱ ከ16፡00-19፡00 የቤተክርስቲያን ሳምንታዊ የፀሎት ፕሮግራም ይካሄዳል። የሥራ ሁኔታ ከማይፈቅድልን ወገኖች ውጪ በፆምና በፀሎት በእግዚአብሄር ፊት እንሆናለን። ሁላችሁም እንድትካፈሉ እናበረታታለን።
-
ዘወትር ቅዳሜ ከ12፡00-15፡00 ረቡዕ ከ15፡00-18፡00 የብሔራዊ ትያትር የቴባን መውጫ ላይ በሕብረት ለወንጌል ሥርጭት ስለሚወጣ ቅዱሳን እንድትሳተፉ ቤተክርስቲያን
ታበረታታለች።
Latest Sermons
የምክርና የፀሎት አገልግሎት ለምትፈልጉ እህቶችና ወንድሞች
በ (+47) 46525737
ስልክ ቁጥር በመደወል ቀጠሮ በማስያዝ መገልገል እንደምትችሉ ቤተክርስትያን ታሳውቃለች።
የቤተክርስትያናችንን ፓስተር (መጋቢ) ማግኘት ከፈለጉ ደግሞ
በ (+47) 97926153
ላይ ደዉለዉ ፓስተር ተመስገን ሽብሩን ማናገር ይችላሉ።
-
የአዲሱ ሕንፃ የምረቃና ታላቅ የምስጋና ፕሮግራም ሜይ 11 እስከ 12 ይደረጋል። ለዚህ ያደረሰንና የረዳን እግዚአብሄር ይመስገን። በዕለቱ የተለያዩ ፕሮግራሞችና ዝግጅቶች ይካሄዳሉ። በእለቱ ሁላችንም ለብሰን የምንመጣው ቲሸርት መሸጥ ተጀምሯል። ሳያልቅብን ሁላችንም መግዛት ይገባል። ከ300 ክሩነር ጀምሮ ሲሆን ከ10 ዓመት በታች ለሆኑ ልጆች አልቋል።
-
የ2024 የአባላት ጠቅላላ ጉባኤ የሚካሄደው እሑድ ግንቦት 18 ቀን ይሆናል።
በእለቱም- የ2023 ዓ.ም. የእንቅስቃሴና የፋይናንስ ሪፖርት ይቀርባል
- በመሪዎች ጉባኤ የሚቀርበው አስመራጭ ኮሚቴ ይፀድቃል
-
ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ በቫይበር የማስታወቂያ መድረክ ላይ እንደተነገረ
የኖርዌይ መንግስት 19 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በግዴታ ወደ
አገራቸው ለመመለስ በሚል በትራንዱም የስደተኞች ማቆያ መያዙን የሚቃወም
ሰላማዊ ሰልፍ በሜኔስከር ኢ ሊምቦ በሚል ድርጅት ተዘጋጅቶ እኛም
እንድሳተፍ ተጋብዘናል። ሰላማዊ ሰልፉም የሚካሄደው ማክሰኞ በ30/04/2024
ከቀኑ 15፡00-17፡00 በEidsvolls plass ፊት ለፊት ነው።